Wednesday, January 22, 2014

አንቶኖቭ 28 አውሮፕላን በለገዳዲ አካባቢ ተከሰከሰ



ንብረትነቱ የዩክሬን የሆነ አንቶኖቭ 28 የመንገደኞች አውሮፕላን ከኡጋንዳ ኢንቴቤ ተነስቶ ወደ ሰንዓ የመን በመብረር ላይ እንዳለ ባለፈው ሰኞ አዲስ አበባ አቅራቢያ ለገዳዲ አካባቢ መከስከሱን ሪፖርተር ጋዜጣ ከአዲስ አበባ ዘገበ። ጋዜጣው ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን አገኘሁት ባለው መረጃ እንደሚያስረዳው፣ የአውሮፕላኑ አብራሪዎች ሰኞ ማለዳ ከባለሥልጣኑ ጋር ባደረጉት የሬዲዮ ግንኙነት ከኢንቴቤ ተነስተው በኢትዮጵያ በኩል ወደ የመን ለመብረር ፈቃድ ጠይቀው ነበር፡፡ ባለሥልጣኑም የበረራ ፈቃድ ሰጥቷቸዋል፡፡

የኢህአዴግ መራሹ መንግስት ለነፃነት የሚሰጠው ትርጓሜ

የኢህአዴግ መራሹ መንግስት ‹መዝገበ ቃላት› ለነፃነት የሚሰጠው ትርጓሜ ‹አራምደዋለሁ› ከሚለው ግራ-ዘመሙ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ብያኔ አንፃር የሚተነተን በመሆኑ፣ የየትኛውም ተቋም ነፃ ሆኖ የመንቀሳቀስ መብት ላይ ረዣዥም እጆቹን ደጋግሞ እየጫነ ሲጨፈልቅና ሲያስጨፈልቅ ለመኖሩ በርካታ ማሳዎችን ማቅረብ ይቻላል።

Monday, January 20, 2014

“ከወረስነው ቂም ይልቅ የምናወርሰው ፍቅር ይበልጣል” ቴዲ አፍሮ



በሳምንቱ መጨረሻ ቴዲ አፍሮ ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ቆይታ ነበረው፡፡ በሁለት ክፍል የተደረገውን ቃለ-ምልልስ የመጀመሪያ ክፍል እነሆ ፡)

Prof. Mesfin Woldemariam

በአለፉት ሃያ ዓመታት ውስጥ ወያኔ-ኢሕአዴግ የሚወቀስበት ሥራ በጣም ቢያመዝንም የሚመሰገንበት ሥራ የጽሑፍ ቁጥጥርን ማስቀረቱ ብቻ ነው፤ ሁልጊዜም አንድ ጥሩ ነገር የሚያስከትለው አብዛኛውን ጊዜ የማይጠበቅ ነገር ሊኖር ይችላል፤ ለምሳሌ

በሃይማኖት ጭቆና ስም የሚረጩ አደገኛ መርዞች

አራተኛውን የኢቲቪ “ጥናታዊ ፊልም” አየሁት፤ ዝቅ ሲል ለምርጫ ቅስቀሳ፣ ከፍ ሲል ደግሞ ከፋፍሎ ለመግዛት ተብሎ የተዘጋጀ ይመስለኛል። ፊልሙ ኢህአዴግንና የቀድሞ ስርዓቶችን ያነጻጽራል፤ ማንም ነፍስ ያለው ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ የሃይማኖት ጭቆና አልነበረም ብሎ አይክድም፤ ልዩነቱ የሚጀመረው “ጨቋኙ ማን ነው? ተጨቋኙስ?” የሚለውን ለመመለስ ሲሞከር ነው።

የአውራው ፓርቲ “ብዥታዎች” በዝተዋል!

የኒዮሊበራሊዝም ኃይሎች በአሸባሪነት ተፈርጀዋል እንዴ?
የኢኮኖሚ ዕድገቱን መካድ “ከሃዲነት” ነው!
“የመንግስት ሚዲያዎች በባህርያቸው የአውራው ፓርቲ ልሳን ሆነዋል”
<እውነቱን ለመናገር በአሁኑ ወቅት “ማጥራት” የሚፈልጉ “ብዥታዎች” እንደ ጉድ ተበራክተዋል (የቃላቱ ኮፒራይት የኢህአዴግ መሆኑ ልብ ይባልልኝ!) እናላችሁ ….. የዛሬ ፖለቲካዊ ወጌ በእነዚህ “ብዥታዎች” ዙርያ ያጠነጥናል፡፡

Sunday, January 19, 2014

ለ1.6 ቢሊዮን ዶላር የቴሌ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አማካሪ ድርጅት ሊቀጠር ነው



ሁለቱ የቻይና ኩባንያዎች ሁዋዌና ዜድቲኢ ለሚያከናወኑት የ1.6 ቢሊዮን ዶላር የሞባይል ኔትወርክ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አማካሪ ድርጅት ለመቅጠር ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጥቷል፡፡
ጨረታውን ያወጣው የፕሮጀክቱ ባለቤት ኢትዮ ቴሌኮም ነው፡፡ የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ አብዱራሂም አህመድ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ አማካሪ ድርጅቱን ለመቅጠር የወጣው ዓለም አቀፍ ጨረታ ጥር 29 ቀን 2006 ዓ.ም. በይፋ ይከፈታል፡፡