
የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በተለይም የስርዓቱ ኣፈቀላጤ የሆኑ ሚዲያዎች ቴዲ ከሃገር አንዳይወጣ የተከለከለው ከዓመታት በፊት ይነዳት የነበረችው መኪና ታክስ ባለመክፈሉ በተከሰሰበት ክስ ነው ቢሉም ቴዲ በዚህ ክስ በዋስ የወጣና ክስም ያልተመሰረተበት ከመሆኑም በላይ ፍርድ ቤቱ ከሃገር አንዲወጣ ፈቃድ የሰጠበትን ወረቀት መያዙ ጉዳዩን ፖለቲካዊ ይዘት አንዲኖረው ኣድርጉዋል።
ቴዲ ፓስፖርቱን የያዙበት ደህንነቶች ትናንት የለቀቁለት በመሆኑ ምናልባትም ችግር ካልገጠመው ወደ ኣውሮፓ ሊጉዋዝ ይችላል ተብሉዋል፥፥ ቴዲ በኣውሮፓ ኦስሎ ነገ የሙዚቃ ኮንሰርቱንም ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። የቴዲ ባንድ ከሆላንድ ወደ ኦስሎ ትናንት ያመሩ ሲሆን በነገው ዕለት የሚደረገው ኮንሰርትም በጉጉት እንደሚጠበቅ ከኖርዌይ ለዘሐበሻ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
No comments:
Post a Comment