Friday, April 4, 2014

በዛሬው ቀን / አፈና እና እሥር ተጠናክሮ ቀጥሏል !!!

በዛሬው ቀን / አፈና እና እሥር ተጠናክሮ ቀጥሏል !!!
ከማለዳው ጀምሮ የአዲስ አበባ ፖሊስ ከኢህአዴግ የተለየ አመለካከት የሚያራምዱ ወጣቶችን እያደነ ማሰሩን ገፍቶበታል፡፡

የታሰሩት የአንድነት አባላት ቁጥር ሥድስት ደርሷል፡፡ ምንም ህጋዊ መሰረት በሌለው የጉልበተኛነት ሥሜት ብቻ የፓርቲ አባላት እየተለቀሙ የሚታሰሩ ከሆነ፤ ኢህአዴግ ከተቃዋሚዎች ጋር በህግ ዳኝነት ለመገላገል ፍቃደኛ ካልሆነ እና ህግ የበላይ ሆኖ ሊዳኘን ካልቻለ የሰላማዊ ትግል እድል ፈንታው ምን ይሆናል የሚል ጥያቄ ተነስቶ ለውይይት መቅረቡ ግድ ይመስለኛል፡፡
መብት አይለመንም !!!
ህዝብ የካድሬ ሎሌ ሊሆን አይገባም !!!

No comments: