Thursday, January 29, 2015

የሰላም በሮች ሲዘጉ የሁለገብ ትግል ስልት በሮች ይከፈታሉ! (አርበኞች ግንቦት7)

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ አማካይነት እየደረሰበት ያለውን በደል ለሕዝብ ለማሰማት ጥር 17 ቀን 2007 ዓም በአዲስ አበባ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ጂንካና ሸዋ ሮቢት የተቃውሞ ሰልፎችን ጠርቶ ነበር። በተለይ በአዲስ አበባው ሰልፍ ላይ የተገኙ ወገኖቻችን ለህወሓት ፍጹም ታማኝ በሆነው የፓሊስ ክፍል ያለርህራሄ መደብደባቸው እና የተቃውሞ ሰልፉም በጉልበት መበተኑ ነፃነትና ፍትህ ናፋቂውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያሳዘነ ብቻ ሳይሆነ ያስቆጨ ጉዳይ ነው።

Sunday, January 11, 2015

Arbegnoch-Ginbot7 for Unity and Democracy Movement merged (አርበኞች-ግንቦት7 የአንድነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ተመሰረተ)

Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy (Ginbot 7) and Ethiopian People’s Patriotic Front (EPPF) merged. The united front will be called “Arbegnoch-Ginbot7 for Unity and Democracy Movement” (አርበኞች-ግንቦት7 የአንድነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ

Tuesday, December 30, 2014

በተለያዩ አገሮች የሚኖሩ የወያኔ አገልጋዮች ስም ዝርዝር

ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ ንብረትና ቤት አልባ አድርጎ በአንጻሩ ደግሞ በውጭ የሚኖረውን ኢትዮጵያዊ በአገሩ ውስጥ ያለውን አፋኝና አምባገነን አገዛዝ እንዳይታገል ለማድረግ በርካታ የማታለያና የማደናገሪያ ዘዴዎችን ይጠቀማል።

የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በወህኒ ቤት ዘረፋ እንደተካሄደባቸው አስታወቁ


የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በወህኒ ቤት ዘረፋ እንደተካሄደባቸው አስታወቁ
‹‹በደምበኞቼ ላይ ዘረፋ ተፈፅሟል›› ጠበቃ ተማም አባቡልጉ
‹‹በህይወቴ ላይ የደህንነት ስጋት አለብኝ›› አቶ ሀብታሙ አያሌው
‹ከፍተኛ በደል ተፈፅሞብኛል›› አቶ ዳንኤል ሺበሺ

በእነ ዘላለም ወርቅነህ የክስ መዝገብ የተከሰሱት አራት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ላይ በወህኒ ቤት ውስጥ በመንግስት የደህንነት አባላት ዘረፋ እንደተካሄደባቸው ለፍርድ ቤት ተናገሩ፡፡

Monday, December 29, 2014

በባህር ዳር የአንድ እንግሊዛዊን ድንገተኛ ሞት

በባህር ዳር የአንድ እንግሊዛዊን ድንገተኛ ሞት እየመረመርኩ ነው ያለው ወያኔ/ኢህአዲግ ”በታህሳስ 9/2007 ዓም የአምስት ሰዎችን ሞት እና የአንድ መነኮሳይትን ጨምሮ የሌሎች በርካታ ኢትዮጵያውያን ደም መፍሰስ ትክክል ነበር” የሚል ሰልፍ እያዘጋጀ ነው.

bahr dar 2ፎቶ -ታህሳስ 9/2007 ዓም የቤተ ክርስቲያን ይዞታን መንግስት ያክብር ብለው ከምዕመናን ጋር ከተሰለፉት ውስጥ በጥይት የተመቱ መነኮሳይት
ወንበዴ መሪ በሆነበት ሀገር ፍትህ መቀለጃ ትሆናለች።ሕግ፣ስርዓት እና ምክንያታዊነትን ዜጎች ቢናፍቁም ህገወጦች ስልጣን ከተቆናጠጡ ዙርያቸውን በሀገር ውስጥ እና በባህር ማዶም ጭምር የሚኮለኩሏቸው ለሆዳቸው እና ለጥቅማቸው ብቻ የሚሰለፉቱን ነውና ብዙ ጆሮ የሚጠልዙ ነገሮችን መስማት ይለመዳል።

Saturday, December 20, 2014

ቴዲ አፍሮ ፓስፖርቱ ተመለሰለት

ላለፉት ፫ ሳምንታት ከሃገር እንዳይወጣ ታግዶ የነበረው ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ ፓስፖርቱ ተመለሰለት። ፍርድ ቤት ሳያዝ ማን እንደከለከለው ሳይታወቅ በድህነንቶች ፓስፖርቱን ተቀምቶ ሲጉላላ የነበረው ቴዲ ኣፍሮ በዚህ የተነሳ በፊንላንድ እና በሆላንድ ኮንሰርቱን ለመሰረዝና የ፫፪ ሺ ዩሮ ኪሳራ ሊደርስበት ችሉዋል።