Wednesday, January 29, 2014

የሀሮማያው ዩኒቨርስቲው ብጥብጥ ዝርዝር መረጃ



በሀሮማያ ዩኒቨርስቲ የቴክኖሎጂ ተማሪዎች የሚማሩበት ገንደጄ የተባለው ግቢ ውስጥ በአሁኑ ሰዓት ከፍተኛ ብጥብጥ እንደተነሳ የተሰማ ሲሆን ፤ ግቢውም በፌደራል ፖሊሶች እንደተከበበ ይገኛል፡፡ ተማሪዎቹ ከቀን ጀምሮ ምግብ ባለመመገብ ተቃውሟቸውን የጀመሩ ሲሆን ፤ በአሁኑ ሰዓትም ሁሉም ተማሪዎች ወደ ዶርም አንገባም በማለት ከፌደራል ፖሊሶች ጋር ተፋጠው ይገኛሉ፡፡ በአከባቢው ላይ ያሉ የሌላ ግቢ ተማሪዎችም ብጥብጡ ከአሁን አሁን ወደኛ ጋር ይመጣል በሚል ስጋት በጭንቀት ውስጥ መሆናቸውም ታውቋል፡፡

“የኢትዮጵያ ፓርቲዎች የሃቀኝነት ጥያቄ ይነሳባቸዋል”



ለ46 ዓመታት በፖለቲካ ትግል ውስጥ እንደቆዩ የሚናገሩት የ70 ዓመቱ አዛውንት የቀድሞ የኢፌዲሪ ኘሬዚዳንት ኋላም

የህወሃት/ኢህአዴግ የሃይል መንገድ የሚያሳየን ድርጅቱ የሐሳብ ምክነት እንዳለበት ነው::

የህወሃት/ኢህአዴግ የሃይል መንገድ የሚያሳየን ድርጅቱ የሐሳብ ምክነት እንዳለበት ነው በአንድነት ፓርቲ የሶስት ወራት ህዝባዊ ንቅናቄ ላይ መሳተፍ መቻሌ አገሪቱን በመምራት ላይ ስለሚገኘው ጡንቸኛው ድርጅት ብዙ ነገሮችን በቅርበት ለማወቅ አስችሎኛል፡፡

በቂ ጥበቃ ያልተደረገለት ሰርግ በሰው ደም ተጨማልቆ ተጠናቀቀ



በዳዊት ሰለሞን
በአዲስ አበባ ሐምሌ 19 መናፈሻ ትናንት 18/05/2006 እሁድ 10፡00 ገደማ በሰርግ ታዳሚዎችና በአካባቢው በሚገኙ ወጣቶች መካከል በተነሳ ግጥት ብዙዎች ክፉኛ ተጎድተው ወደ የካቲትና ምኒልክ ሆስፒታሎች መወሰዳቸውን በሰርጉ የታደሙ ሰዎች ለፍኖተ ነጻነት ተናግረዋል፡፡

መንግስታት ፈለጉት ኣልፈለጉት በኤርትራና በኢትዮጵያ ህዝቦች መካከል ለወደፊት ትውልዶች የሚቀጥል የመዋሃድ ዝምድና መኖር ኣለበት” ኢሳያስ ኣፈወርቂ



ኣቶ ኢሳያስ ኣፈወርቂ
ከኣሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ጣቢያ ያማርኛው ክፍል
ከጋዜጠኛ ኣዳነች ፍስሃየ ጋር ያደረገው ቃለ መጠይቅ
ጋዜጠኛ ኣዲሱ ኣበበ፥ እየተገባደደ የነበረውን የኣውሮጳውያን የ1992 ዓ.ም. ምክንያት በማድረግ በተገባደደው ዓመት

በ6 የሱዳን ወጣቶች የተደፈረችው ኢትዮጵያዊት በእስር ላይ እንደምትገኝ ታወቀ

ኢሳት ዜና :-ቀድሪያ እንድሪስ የተባለች ኢትዮጵያዊት ወጣት በ6 የሱዳን ወጣቶች እጅግ አሰቃቂ በሆነ መንገድ ስትደፈር የሚያሳይ ቪዲዮ ኢሳት የደረሰው ሲሆን ፣ ካርቱም የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ የዲያስፖራ ክፍል ሃላፊ የሆኑት አቶ አረጋ ልጂቷ መደፈሩዋን አምነው ተጨማሪ መረጃ ለመስጠት ግን ከፍተኛ ባለስልጣኖች መፍቀድ አለባቸው በሚል ዝርዝር ጥያቄዎችን ለመመለስ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።

Monday, January 27, 2014

የኦህዴድ ውስጥ ውስጡን መደራጀት ሕወሓትን አሳስቦታል፤


የብኣዴን እና የኦሕዴድ ባለስልጣናት ቅርርብ አልተመቸውም፤ «...አደጋ ውስጥ ነን።» የሕወሓት የደሕንነት መሪዎች

በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ከፍተኛ የሆኑ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ከፍተኛ ባለስልጣናት መቀራረብ እና አብሮ መዋል የሕወሓት ሰዎችን ማሳሰቡን እና

የኢትዮጵያ ወታደሮች አሚሶምን ተቀላቀሉ

የኢትዮጵያ ወታደሮች ሶማሊያ ውስጥ ከሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል – አሚሶም ጋር በይፋ ተቀላቀሉ፡፡
ameson
የኢትዮጵያ ወታደሮች ሶማሊያ ውስጥ ከሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል – አሚሶም ጋር በይፋ ተቀላቀሉ፡፡

ሂውማን ራይትስ ዎች በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩ ይበልጥ ጠቧል




መንግስት፤ ተቋሙ የተቃዋሚዎች የፕሮፖጋንዳ ማስፈፀሚያ ነው
“በኢትዮጵያ የነፃ ሚዲያ ህልውና አደጋ ላይ ነው”
“በኤርትራ የመብት ጥያቄ ማንሳት ነውር ሆኗል” ብሏል

Sunday, January 26, 2014

We hate weyane.......

The difference!!!!

Free Reeyot Alemu and all journalist prisoners

ሌባ ሆዷም ባንዷ ይሂ ነው

የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ Ethiopian Youth National Movement

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት ጥሪ የሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ጥሪ ነው! 

የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ በኢትዮጵያ አስተማማኝ የሆነ የህዝብ የበላይነት፣ ነፃነት፣ ፍትህ፣ እኩልነት፣ የህግ የበላይነትና፣ 

U.S.A -Bring Jawar Mohammed to Justice. Petition

To be delivered to The United States House of Representatives and The United States Senate
A Muslim extremist currently advocating hate, genocide , ethnic cleansing and violence against non-oromos and non-muslim in Ethiopia. 

“Time to bring back Eritrea from the cold”

HRW- 2014 WORLD REPORT

Hopes that Ethiopia’s new leadership would pursue human rights reforms following Prime Minister Meles Zenawi’s death in August 2012 have been shattered; there was no tangible change of policy in 2013. Instead, the Ethiopian authorities continue to severely restrict the rights to freedom of expression, association, and peaceful assembly, using repressive laws to constrain civil society and independent media, and target individuals with politically motivated prosecutions.

የእነ አንዱዓለም አራጌ ቀጠሮ ተምታታ



ፍርድ ቤቱ ለጥር 30 ቀጥሯቸዋል፤ ሬጅስትራር በበኩሉ ጥር 24 ቀን 2006ዓ.ም መቅረብ አለባቸው ይላል፤

BREAKING NEWS ኣብራሃ ደስታንና አቶ አስገደ ገ/ስላሴን ጨምሮ አምስት የዓረና ኣባላት መደብደባቸው ተነገረ።



ዓረና ትግራይ በመጬው እሁድ በዓዲግራት ለጠራው ህዝባዊ ስብሰባ በመቀስቀስ ላይ የነበሩት የስ/አስፈፃሚ ኣባል አብርሃ ደስታ፤ መስራች አቶ አስገደ ገ/ስላሴ፤ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወጣት ዓምዶም ገ/ስላሴና ሌሎች ሁለት የፓርቲው አባላት ማንነታቸው ባልታወቁ ግለሰቦች በድንጋይ መደብደባቸው ተሰማ።

ሱማሊያዊት ኢትዮጲያ (አሌክስ አብርሃም )



ይሄውላችሁ ዛሬ ቤት ለቀኩ !! ምርጧን ቅዳሜ እቃ ከዛ ከዚህ በማንዘፋዘፍና ‹‹ቆምጨ›› ጋር በመነታረክ እንዳሳለፍኳት ስነግራችሁ በታላቅ ደስታ ነው ! ምክንያቱም ቅዳሜ ቀን ምንም ይፈጠር ምን ቅዳሜ መሆኑ በራሱ አንዳች የሰላም ስሜት አለውና …. ብለን ቅዳሜያችንን የነጀሱትን ነገራ ነገሮች ሁሉ አፉ ካልን በኋላ ስለነበረው ነገር ጨዋታችንን እንቀጥላለን ! (አሌክስ አብርሃም ነኝ ከአዲሱ ቤቴ ልበል እንዴ? )

Wednesday, January 22, 2014

በርካታ ሙስሊሞች “ሕዝብን ለሽብር ቀስቅሻለሁ” ብላችሁ እመኑ በሚል በእስር ቤት እየተገረፉ መሆኑ ተዘገበ

ህወሐት መራሹ የኢትዮጽያ መንግስት ሕዝበ ሙስሊሙ ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደቀጠለ ነው ሲል ቢቢኤን ራድዮ ዘገበ። እንደ ራድዮው ዘገባ ከኢዱ ጅምላ ጭፍጨፋ ቡኋላ መንግስት ልዩ ግብረ ኃይል በማቋቋም በአ/አበባ በወልቂጤ እንዲሁም በአዳማ ከተማዎች ላይ የሚገኙ መስጂድ የሚያዘወትሩ ወጣቶችን ከየቦታው አፍኖ በመውሰድ በአገራችን ጏንታናሞ ማእከላዊ እስር ቤት ውስጥ “ሕዝብን ለሽብር ቀስቅሻለሁ” ብላችሁ እመኑ እየተባሉ ቀን ከሌት የስቃይ አይነት ሲያስቆጥራችው ከርሞ ጥር 7 2006 ቁጥራቸው 16 የሚደርሱ ወጣቶችን የወያኔ ፋሽን የሆነውን የሽብርተኝነት ክስ መስርቶ ወደ ቂሊንጦ (ሒጅራ ኮምፓውንድ ) አዛውሯቸዋል::

ከሱዳን ጋር የሚደረገው የድንበር ውዝግብ የሞራልና የሶሻል ጥያቄ እንጅ የህግ ድጋፍ የለውም ሲሉ አንድ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣን ተናገሩ

ኢሳት ዜና :-ባለስልጣኑ ይህን የተናገሩት የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የደህንነት ሰራተኞች በተገኙበት በተደረገው ግምገማና ውይይት ላይ ነው።
በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ያለውን ድንበር የማካለል እንቅስቃሴ ከ1965 ዓም ጀምሮ በጊዜው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር በነበሩት ዶ/ር ምናሴ ሃይሌና በሱዳኑ አቻቸው ጃፋር ኤሊ ሜሪ መካከል የተጀመረ እና እስካሁኑም የዘለቀ መሆኑን ባለስልጣኑ አውስተዋል።

በቦረና ኦሮሞና በቡርጂዎች መካከል በተነሳ ግጭት ሰዎች እየተሰደዱ ነው

ቦረና አከባቢ የሚኖሩ ቡርጂዎች እየተሰደዱ ነው፡፡ ከአከባቢው ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው የግጭቱ መንስኤ በቡርጂ መንደር ተገድሎ ተገኘ ተባለ የቦረና ብሄረሰብ አባል አስከሬን ነው፡፡

አንቶኖቭ 28 አውሮፕላን በለገዳዲ አካባቢ ተከሰከሰ



ንብረትነቱ የዩክሬን የሆነ አንቶኖቭ 28 የመንገደኞች አውሮፕላን ከኡጋንዳ ኢንቴቤ ተነስቶ ወደ ሰንዓ የመን በመብረር ላይ እንዳለ ባለፈው ሰኞ አዲስ አበባ አቅራቢያ ለገዳዲ አካባቢ መከስከሱን ሪፖርተር ጋዜጣ ከአዲስ አበባ ዘገበ። ጋዜጣው ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን አገኘሁት ባለው መረጃ እንደሚያስረዳው፣ የአውሮፕላኑ አብራሪዎች ሰኞ ማለዳ ከባለሥልጣኑ ጋር ባደረጉት የሬዲዮ ግንኙነት ከኢንቴቤ ተነስተው በኢትዮጵያ በኩል ወደ የመን ለመብረር ፈቃድ ጠይቀው ነበር፡፡ ባለሥልጣኑም የበረራ ፈቃድ ሰጥቷቸዋል፡፡

የኢህአዴግ መራሹ መንግስት ለነፃነት የሚሰጠው ትርጓሜ

የኢህአዴግ መራሹ መንግስት ‹መዝገበ ቃላት› ለነፃነት የሚሰጠው ትርጓሜ ‹አራምደዋለሁ› ከሚለው ግራ-ዘመሙ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ብያኔ አንፃር የሚተነተን በመሆኑ፣ የየትኛውም ተቋም ነፃ ሆኖ የመንቀሳቀስ መብት ላይ ረዣዥም እጆቹን ደጋግሞ እየጫነ ሲጨፈልቅና ሲያስጨፈልቅ ለመኖሩ በርካታ ማሳዎችን ማቅረብ ይቻላል።

Monday, January 20, 2014

“ከወረስነው ቂም ይልቅ የምናወርሰው ፍቅር ይበልጣል” ቴዲ አፍሮ



በሳምንቱ መጨረሻ ቴዲ አፍሮ ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ቆይታ ነበረው፡፡ በሁለት ክፍል የተደረገውን ቃለ-ምልልስ የመጀመሪያ ክፍል እነሆ ፡)

Prof. Mesfin Woldemariam

በአለፉት ሃያ ዓመታት ውስጥ ወያኔ-ኢሕአዴግ የሚወቀስበት ሥራ በጣም ቢያመዝንም የሚመሰገንበት ሥራ የጽሑፍ ቁጥጥርን ማስቀረቱ ብቻ ነው፤ ሁልጊዜም አንድ ጥሩ ነገር የሚያስከትለው አብዛኛውን ጊዜ የማይጠበቅ ነገር ሊኖር ይችላል፤ ለምሳሌ

በሃይማኖት ጭቆና ስም የሚረጩ አደገኛ መርዞች

አራተኛውን የኢቲቪ “ጥናታዊ ፊልም” አየሁት፤ ዝቅ ሲል ለምርጫ ቅስቀሳ፣ ከፍ ሲል ደግሞ ከፋፍሎ ለመግዛት ተብሎ የተዘጋጀ ይመስለኛል። ፊልሙ ኢህአዴግንና የቀድሞ ስርዓቶችን ያነጻጽራል፤ ማንም ነፍስ ያለው ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ የሃይማኖት ጭቆና አልነበረም ብሎ አይክድም፤ ልዩነቱ የሚጀመረው “ጨቋኙ ማን ነው? ተጨቋኙስ?” የሚለውን ለመመለስ ሲሞከር ነው።

የአውራው ፓርቲ “ብዥታዎች” በዝተዋል!

የኒዮሊበራሊዝም ኃይሎች በአሸባሪነት ተፈርጀዋል እንዴ?
የኢኮኖሚ ዕድገቱን መካድ “ከሃዲነት” ነው!
“የመንግስት ሚዲያዎች በባህርያቸው የአውራው ፓርቲ ልሳን ሆነዋል”
<እውነቱን ለመናገር በአሁኑ ወቅት “ማጥራት” የሚፈልጉ “ብዥታዎች” እንደ ጉድ ተበራክተዋል (የቃላቱ ኮፒራይት የኢህአዴግ መሆኑ ልብ ይባልልኝ!) እናላችሁ ….. የዛሬ ፖለቲካዊ ወጌ በእነዚህ “ብዥታዎች” ዙርያ ያጠነጥናል፡፡

Sunday, January 19, 2014

ለ1.6 ቢሊዮን ዶላር የቴሌ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አማካሪ ድርጅት ሊቀጠር ነው



ሁለቱ የቻይና ኩባንያዎች ሁዋዌና ዜድቲኢ ለሚያከናወኑት የ1.6 ቢሊዮን ዶላር የሞባይል ኔትወርክ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አማካሪ ድርጅት ለመቅጠር ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጥቷል፡፡
ጨረታውን ያወጣው የፕሮጀክቱ ባለቤት ኢትዮ ቴሌኮም ነው፡፡ የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ አብዱራሂም አህመድ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ አማካሪ ድርጅቱን ለመቅጠር የወጣው ዓለም አቀፍ ጨረታ ጥር 29 ቀን 2006 ዓ.ም. በይፋ ይከፈታል፡፡ 

ግራና ቀኝ ጠፋን! ፕ/መስፍን ወልደ ማርያም



በአለፉት ሃያ ዓመታት ውስጥ ወያኔ-ኢሕአዴግ የሚወቀስበት ሥራ በጣም ቢያመዝንም የሚመሰገንበት ሥራ የጽሑፍ ቁጥጥርን ማስቀረቱ ብቻ ነው፤ ሁልጊዜም አንድ ጥሩ ነገር የሚያስከትለው አብዛኛውን ጊዜ የማይጠበቅ ነገር ሊኖር ይችላል፤ ለምሳሌ አጠቃላይ ነጻነት ሲመጣ ወንጀለኛነት ይጨምራል፤ እንዲሁም የጽሑፍ ቁጥጥር ሲነሣ ጸሐፊዎች ይበዛሉ፤ ትምህርት በተስፋፈበትና ማንም እንደፈለገ ለመጻፍና ለማሳተም ችሎታውም ዕድሉም በማይገኝበት፣ ሳያበጥርና ሳይሰልቅ አሰር-ገሰሩን ጽፎ በአደባባይ የሚወጣውን ጥምብ-እርኩሱን አውጥተው ሁለተኛ እንዳይለምደው የሚያደርጉ የታወቁና የሰላ አእምሮና ብዕር ያላቸው አርታእያንና ሐያስያን (ገምጋሚዎች) ባሉበት ብዕሩን የሚያባልግ ጸሐፊ አይወጣም፤ ይህ ሁሉ ባልተሟላበት እንደኛ ባለ አገር ውስጥ ብዕርን ማባለግ እንደመብት ወይም እንደነጻነት እየታየ ነው፡፡

በህይወት የሚገኙ አካለ ሰንኩላን እህቶቻችን እና ባለቤት አልባው የዜጎቻችን ሬሳ ብሶት በሳውዲ አረቢያ ሆስፒታሎች ።

ላለፉት ተከታታይ ፫ ሳምንታት በርካት ኢትዮጵያውያን ከ ሳውዲ አረብያ ጂዛን፡ወደ አዲስ አበባ በቀጥታ በረራ እየተሸኙ ሲሆን በመኪና አደጋ እና መሰል ተዛማጅ አደጋዎች ቆመው መራመድ የማይችሉ ወገኖቻችን በሳውዲ አየርላይንስ እንደማይጫኑ በመግለጹ ለከፍተኛ የሞራል ዝቅጠት መዳረጋቸውን ምንጮች ይገልጻሉ።በተለይ በጂዛን ከተማ በአቡሰዳድ ኣድ ደርብ ሆስፒታል ለ፫ አመታት ያልጋ ቁራኛ እንደሆነች የሚነገርላት ወጣት ከዲጃ መሓመድ ሑሴንን አብነት የሚጠቅሱት እነዚህ ምንጮች ።

የቀድሞ የኦነግ አመራር ሌንጮ ለታ፣ አዲስ ፓርቲ ይዘው አዲስ አበባ ገቡ

ዶ/ር ነጋሶ የአቶ ሌንጮ መመለስ በበጐ የሚታይ ነው ብለዋል

በኢትዮጵያ መንግስት “ሽብርተኛ ተብሎ የተሰየመው የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር /ኦነግ/ ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ሌንጮ ለታ፣ አዲስ ያቋቋሙትን ፓርቲ ይዘው በሰላማዊ መንገድ ለመታገል አዲስ አበባ መግባታቸውን ምንጮች ገለፁ፡፡

የኢትዮጵያን ታሪክ ጥላሸት የመቀባት አባዜ (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ ጥር 7 ቀን 2006 ዓ.ም
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው ገዥው አካል በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ንጉስ የነበሩት የዳግማዊ አጼ ምኒልክ መቶኛ የሙት ዓመት በዚህ በያዝነው ዓመት (በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር) እየተከበረ ባለበት ወቅት ሙሉ ጊዜውን በመስጠት ንጉሱ የሰሩትን ታላቅ ስራ ሁሉ በማጣጣል እና ጥላሸት በመቀባት ዘመቻ ላይ በመጠመድ ታሪክ የማጠልሸት ድራማውን በመተወን ላይ ይገኛል፡፡

የፊንላንድ ጋዜጠኞች እና የፓርላማ አባላት ከኮሚሽነሮቹ ጋር ተወያዩ

January 19/2014

ሚዲያዎች ሙስናን በብቃት እያጋለጡ አይደለም ተባለ

ሚዲያዎች ሙስናን በብቃት እያጋለጡ አይደለም ተባለ የፊንላንድ ጋዜጠኞችና የፓርላማ አባላት ከኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን፣ ከእንባ ጠባቂ እና ከፀረ ሙስና ኮሚሽን የስራ ሃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ ስላለው የሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የምርጫ ጉዳይ የፀረ ሙስናን እንቅስቃሴ በተመለከተ ተወያዩ፡፡

Saturday, January 18, 2014

ክህደት ከአናት ሲጀምር:- በቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ውስጥ

እውነት ቤት ሥትሰራ …
ውሸት ላግዝ ካለች
ሚስማር ካቀበለች
ጭቃ ካራገጠች
ቤቱም አልተሰራ … እውነትም አልኖረች ።
… እንደዚያ ነው በባቢሎን ዘመን ።
የአንዱ ቋንቋ ከአንደኛው ይዘበራረቃል ….. መግባባትና መረዳዳት ብርቅ ይሆናል ። በጠራ አማርኛ የተጣፈውን በጉግማንጉግኛ በመተርጐም ከውስጡ የሚፈልጉትን ብቻ አለፍ አለፍ እያሉ ያነቡታል ። እናም የራሳቸውን ትርጉም ይሰጡታል ። ፍየል ወድያ ….. ቅዝምዝምም ወዲህ ይሆናል ።